አዋሽ ባንክ በባሌ ሮቤ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ አስመረቀ

በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች የራሱን ህንፃ በመገንባት የሚታወቀው አዋሽ ባንክ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በባሌ ዞን በሮቤ ከተማ ያስገነባውን ባለ 4 ወለል ዘመናዊ ሕንጻ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች በተገኙበት በድምቀት በማስመረቅ ለአገልግሎት አብቅቷል፡፡
የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ባላቸው የቱሪስት መስህቦችና በምርታማነቱ በሚታወቀው የባሌ ዞን መዲና በሆነችው የሮቤ ከተማ የተገነባው ይህ ህንጻ የተገነባበት አካባቢ ለንግድና ለተለያዩ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች ተፈላጊ ሥፍራ በመሆኑ ለሀገሪቱ ብሎም ለክልሉ ያለው የኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

Apr 30, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.9193 58.0577
GBP
68.1105 69.4727
EUR
61.0061 62.2262
AED
14.0233 14.3038
SAR
13.7339 14.0086
CHF
59.6356 60.8283

Exchange Rate
Close