የታታሪዎቹ ውድድር አሸናፊዎች ሽልማታቸውን ተረከቡ

ግንቦት 22 ቀን 2015 ዓ.ም አዋሽ ባንክ፣ በሀገራችን የሚሰተዋለውን የስራ አጥነት ችግርን በመፍታት ረገድ ከፍተኛ ድርሻ እንደሚኖረው የሚታመነው የ “ታታሪዎቹ” ፕሮጀክት ላይ በርካታ ወጣቶች በመሳተፍ የቢዝነስ ሙያ ስልጠና ተጠቃሚ ከመሆናቸውም በተጨማሪ ለተከታታይ ሳምንታት የቴሌቪዥን የስርጭት ሽፋን በነበረው የስራ ፈጠራ ሀሳብ ውድድር ላይም በናሙና (prototype) የተደገፈ ስራዎቻቸውን በማቅረብና ብርቱ ፉክክር በማድረግ በዳኞች ውሳኔ መሰረት ከ 1 – 5ኛ ደረጃዎች ውስጥ ለገቡ አሸናፊዎች ለእያንዳንዳቸው ማለትም ለ1ኛ ደረጃ አሸናፊ የብር 1 ሚሊዮን፣ 2ኛ ለወጣው አሸናፊ የብር 700 ሺህ፣ ለ3ኛ የብር 500 ሺህ፣ ለ4ኛ የብር 300 ሺህ እንዲሁም 5ኛ ደረጃ ላይ ለሚገኘው ተወዳዳሪ የብር 200 ሺህ የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል እንዲሁም ከዋስትና ነፃ እስከ ብር 5 ሚሊዮን ብድር እንደየ ፕሮጀክታቸው ሁኔታ ተመቻችቶላቸዋል ፡፡
ባንኩ በስካይ ላይት ሆቴል ባካሄደው የታታሪዎቹ ውድድር የማጠቃለያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እንደገለፁት የኮርፖሬት ማህበራዊ ሃላፊነት አካል የሆነው የታታሪዎቹ ፐሮጀክት ለወደፊቱም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅሰዋል፡፡ በሥነ ሥርዓቱ ላይ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችን ጨምሮ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

Sep 21, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
55.1948 56.2987
GBP
65.1720 66.4754
EUR
59.0308 60.2114
AED
13.5981 13.8701
SAR
13.3154 13.5817
CHF
58.7571 59.9322

Exchange Rate
Close