አዋሽ ባንክ የ2022/23 ዓመታዊ የሥራ አመራር ስብሰባ አካሄደ

አዋሽ ባንክ የ2022/23 ዓመታዊ የሥራ አመራር ስብሰባ ሐምሌ 28 እና 29 ቀን 2015 ዓ.ም በእስካይ ላይት ሆቴል አካሂዷል።

የአዋሽ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራዉ በጉባኤው የመክፈቻ ንግግር ላይ እንደ ገለፁት ባንኩ ባጠናቀቀዉ ሂሳብ ዓመት አመርቂ ውጤት ሊያስመዘግብ የቻለው ሊፍጠሩ የሚችሉ ተግዳሮቶችን ለመከላከል ያወጣውን እስትራቴጂ በአግባቡ በመከተልና በመተግበሩ ነው ብለዋል::

ባንኩ በተጠናቀቀዉ የሂሳብ ዓመት ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት የግል ባንኮች መካከል በሁሉም የባንኪንግ የስራ ዘርፎች የመሪነት ስፍራውን እንደያዘ የቀጠለ ሲሆን ይህንን ለማስቀጠል ባንኩ የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል ከፍተኛ መዋለ ንዋይ ፈሰስ በማድረግና ዘርፉን በሚደግፍ ቴክኖሎጂ በመታገዝ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ አክለዋል:: በመጨረሻም በተጠናቀቀዉ ሂሳብ ዓመት አመርቂ ውጤት ላስመዘገቡት ና የቀጠና ጽ/ቤቶች እና ቅርንጫፎች ዕውቅናና የማበረታቻ ሽልማት በማበርከት ስብሰባውን አጠናቋል::

Jul 26, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
57.4895 58.6393
GBP
70.6759 72.0894
EUR
62.3359 63.5826
AED
14.1646 14.4479
SAR
13.8682 14.1456
CHF
62.5028 63.7529

Exchange Rate
Close