አዋሽ ባንክ የ2022/23 ዓመታዊ የሥራ አመራር ስብሰባ አካሄደ

አዋሽ ባንክ የ2022/23 ዓመታዊ የሥራ አመራር ስብሰባ ሐምሌ 28 እና 29 ቀን 2015 ዓ.ም በእስካይ ላይት ሆቴል አካሂዷል።

የአዋሽ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራዉ በጉባኤው የመክፈቻ ንግግር ላይ እንደ ገለፁት ባንኩ ባጠናቀቀዉ ሂሳብ ዓመት አመርቂ ውጤት ሊያስመዘግብ የቻለው ሊፍጠሩ የሚችሉ ተግዳሮቶችን ለመከላከል ያወጣውን እስትራቴጂ በአግባቡ በመከተልና በመተግበሩ ነው ብለዋል::

ባንኩ በተጠናቀቀዉ የሂሳብ ዓመት ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት የግል ባንኮች መካከል በሁሉም የባንኪንግ የስራ ዘርፎች የመሪነት ስፍራውን እንደያዘ የቀጠለ ሲሆን ይህንን ለማስቀጠል ባንኩ የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል ከፍተኛ መዋለ ንዋይ ፈሰስ በማድረግና ዘርፉን በሚደግፍ ቴክኖሎጂ በመታገዝ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ አክለዋል:: በመጨረሻም በተጠናቀቀዉ ሂሳብ ዓመት አመርቂ ውጤት ላስመዘገቡት ና የቀጠና ጽ/ቤቶች እና ቅርንጫፎች ዕውቅናና የማበረታቻ ሽልማት በማበርከት ስብሰባውን አጠናቋል::

Nov 28, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
55.6854 56.7991
GBP
67.1870 68.5307
EUR
60.9588 62.1780
AED
13.7216 13.9960
SAR
13.4363 13.7050
CHF
60.3764 61.5839

Exchange Rate
Close