አዋሽ ባንክ የስራ እድል ፈጠራን የሚያበረታታ የ ‘ታታሪዎቹ’/ ቀጠሌዋን የሁለተኛ ዙር ፕሮጀክት ይፋ አደረገ

አዋሽ ባንክ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ከመወጣት አኳያ ስራ ፈጣሪዎችንና ወጣት ትውልድን ለማበረታታትና ተገቢውን የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችለውን ፕሮጀክት ቀርጾ ወደ ትግበራ መግባቱን ይፋ አድርጓል፡፡
በተካሄደው ሁለተኛው ዙር የ ‘ታታሪዎቹ’/ ቀጠሌዋን የስራ ፈጠራ ውድድር ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት ላይ የባንኩ ዋና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እንደገለፁት ስራ ፈጣሪ የሆኑ ዜጎቻችን በተለይም ወጣት ወንዶችና ሴት እህቶቻችን የእድሉ ተጠቃሚ በመሆን የቢዝነስ ሀሳባቸውን ዕውን በማድረግ በአገራቸው ዕድገት ላይ የራሳቸውን አሻራ እንዲያሳርፉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
የተወዳዳሪ ስራ ፈጣሪዎች ከጥቅምት 12 እስከ ህዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም በበይነ መረብ (ኦን ላይን) ወይንም በሁሉም አዋሽ ባንክ ቅርንጯፎች በአካል በመገኘት ማመልከት እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡

Jul 26, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
57.4895 58.6393
GBP
70.6759 72.0894
EUR
62.3359 63.5826
AED
14.1646 14.4479
SAR
13.8682 14.1456
CHF
62.5028 63.7529

Exchange Rate
Close