አዋሽ ባንክ የስራ እድል ፈጠራን የሚያበረታታ የ ‘ታታሪዎቹ’/ ቀጠሌዋን የሁለተኛ ዙር ፕሮጀክት ይፋ አደረገ

አዋሽ ባንክ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ከመወጣት አኳያ ስራ ፈጣሪዎችንና ወጣት ትውልድን ለማበረታታትና ተገቢውን የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችለውን ፕሮጀክት ቀርጾ ወደ ትግበራ መግባቱን ይፋ አድርጓል፡፡
በተካሄደው ሁለተኛው ዙር የ ‘ታታሪዎቹ’/ ቀጠሌዋን የስራ ፈጠራ ውድድር ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት ላይ የባንኩ ዋና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እንደገለፁት ስራ ፈጣሪ የሆኑ ዜጎቻችን በተለይም ወጣት ወንዶችና ሴት እህቶቻችን የእድሉ ተጠቃሚ በመሆን የቢዝነስ ሀሳባቸውን ዕውን በማድረግ በአገራቸው ዕድገት ላይ የራሳቸውን አሻራ እንዲያሳርፉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
የተወዳዳሪ ስራ ፈጣሪዎች ከጥቅምት 12 እስከ ህዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም በበይነ መረብ (ኦን ላይን) ወይንም በሁሉም አዋሽ ባንክ ቅርንጯፎች በአካል በመገኘት ማመልከት እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡

Nov 28, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
55.6854 56.7991
GBP
67.1870 68.5307
EUR
60.9588 62.1780
AED
13.7216 13.9960
SAR
13.4363 13.7050
CHF
60.3764 61.5839

Exchange Rate
Close