አዋሽ ባንክ የስራ እድል ፈጠራን የሚያበረታታ የ ‘ታታሪዎቹ’/ ቀጠሌዋን የሁለተኛ ዙር ፕሮጀክት ይፋ አደረገ

አዋሽ ባንክ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ከመወጣት አኳያ ስራ ፈጣሪዎችንና ወጣት ትውልድን ለማበረታታትና ተገቢውን የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችለውን ፕሮጀክት ቀርጾ ወደ ትግበራ መግባቱን ይፋ አድርጓል፡፡
በተካሄደው ሁለተኛው ዙር የ ‘ታታሪዎቹ’/ ቀጠሌዋን የስራ ፈጠራ ውድድር ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት ላይ የባንኩ ዋና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እንደገለፁት ስራ ፈጣሪ የሆኑ ዜጎቻችን በተለይም ወጣት ወንዶችና ሴት እህቶቻችን የእድሉ ተጠቃሚ በመሆን የቢዝነስ ሀሳባቸውን ዕውን በማድረግ በአገራቸው ዕድገት ላይ የራሳቸውን አሻራ እንዲያሳርፉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
የተወዳዳሪ ስራ ፈጣሪዎች ከጥቅምት 12 እስከ ህዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም በበይነ መረብ (ኦን ላይን) ወይንም በሁሉም አዋሽ ባንክ ቅርንጯፎች በአካል በመገኘት ማመልከት እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡

Oct 25, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
119.2055 121.5896
GBP
146.5477 149.4786
EUR
129.2543 131.8394
AED
29.3709 29.9583
SAR
28.7559 29.3311
CHF
129.6006 132.1926

Exchange Rate
Close