አዋሽ ባንክ እና አዋሽ ኢንሹራንስ ኩባንያ አረንገጓዴ አሻራቸውን አኖሩ

የእህት ኩባንያዎቹ አዋሽ ባንክ እና አዋሽ ኢንሹራንስ ሠራተኞች በዛሬው እለት ሐምሌ 01 ቀን 2015 ዓ.ም ለአምስተኛው ዙር የአረንጓዴ አሻራ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከቦሌ ክፍለ ከተማ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በአይሲቲ ፓርክ 20 ሺህ ችግኞችን በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል፡፡

እህት ኩባንያዎቹ በኮርፖሬት ማህበራዊ ኃላፊነት መርሐ ግብራቸው በስፋት ከሚሳተፉባቸው ተግባራት አንዱ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን መደገፍ ሲሆን በተለይ ባለፉት 29 ዓመታት ውስጥ በሀገራችን የልማትና የምጣኔ ሀብት ዕድገት ውስጥ አሻራቸውን ካስቀመጡት የግል የፋይናንስ ተቋማት መካከል ግንባር ቀደም መሆናቸው ይታወቃል፡፡

Oct 17, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
119.0155 121.3958
GBP
146.3141 149.2403
EUR
129.0483 131.6293
AED
29.3241 29.9105
SAR
28.7101 29.2843
CHF
129.3940 131.9819

Exchange Rate
Close