አዋሽ ባንክ “አዋሽ ለሁሉም” የተሰኘ ዲጂታል አነስተኛ የብድር አገልግሎት ይፋ አደረገ

ህዳር 24 ፣ 2016 ዓ.ም (አዲስ አበባ)፣ አዋሽ ባንክ “አዋሽ ለሁሉም” የተሰኘ አነስተኛ የብድር አገልግሎት የሚያገኙበት ዲጂታል የብድር አገልግሎት በዛሬው እለት የተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት አካላት እና እንግዶች በተገኙበት በኢሊሊ ሆቴል ይፋ አድርጓል።

በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፉና ዘመኑን የዋጁ የባንክ አገልግሎቶችን በመስጠት ተደራሽነቱን በማስፋት ላይ የሚገኘው አዋሽ ባንክ የደንበኞቹን ፍላጎት ለማርካት ደንበኞች ባሉበት ሆነው አነስተኛ የብድር አገልግሎት የሚያገኙበት “አዋሽ ለሁሉም” የተሰኘውን አገልግሎት እንዲሁም የሳኮስ አይቲ ሶሉዩሽን (SACCOs IT Solution) ቴክኖሎጂ ዛሬ ይፋ ሆኗል።

በሥነ-ስርዓቱ ላይ የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እንደገለፀት አዋሽ ባንክ በኢንዱስትሪው ውስጥ ያለውን የመሪነት ስፍራውን ይዞ እንዲቀጥልና የደንበኞቹን ፍላጎት ለማሟላት በየጊዜው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ተግባራዊ እንደሚያደርግ አመላክተዋል፡፡

Oct 25, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
119.2055 121.5896
GBP
146.5477 149.4786
EUR
129.2543 131.8394
AED
29.3709 29.9583
SAR
28.7559 29.3311
CHF
129.6006 132.1926

Exchange Rate
Close