አዋሽ ባንክ “አዋሽ ለሁሉም” የተሰኘ ዲጂታል አነስተኛ የብድር አገልግሎት ይፋ አደረገ

ህዳር 24 ፣ 2016 ዓ.ም (አዲስ አበባ)፣ አዋሽ ባንክ “አዋሽ ለሁሉም” የተሰኘ አነስተኛ የብድር አገልግሎት የሚያገኙበት ዲጂታል የብድር አገልግሎት በዛሬው እለት የተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት አካላት እና እንግዶች በተገኙበት በኢሊሊ ሆቴል ይፋ አድርጓል።

በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፉና ዘመኑን የዋጁ የባንክ አገልግሎቶችን በመስጠት ተደራሽነቱን በማስፋት ላይ የሚገኘው አዋሽ ባንክ የደንበኞቹን ፍላጎት ለማርካት ደንበኞች ባሉበት ሆነው አነስተኛ የብድር አገልግሎት የሚያገኙበት “አዋሽ ለሁሉም” የተሰኘውን አገልግሎት እንዲሁም የሳኮስ አይቲ ሶሉዩሽን (SACCOs IT Solution) ቴክኖሎጂ ዛሬ ይፋ ሆኗል።

በሥነ-ስርዓቱ ላይ የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እንደገለፀት አዋሽ ባንክ በኢንዱስትሪው ውስጥ ያለውን የመሪነት ስፍራውን ይዞ እንዲቀጥልና የደንበኞቹን ፍላጎት ለማሟላት በየጊዜው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ተግባራዊ እንደሚያደርግ አመላክተዋል፡፡

Sep 07, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
115.1001 118.7426
GBP
141.5006 145.9786
EUR
124.8029 128.7525
AED
28.3594 29.2569
SAR
27.7656 28.6444
CHF
125.1372 129.0973

Exchange Rate
Close