አዋሽ ባንክ በባሌ ሮቤ ከተማ ያስገነባውን ህንፃ አስመረቀ

በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች የራሱን ህንፃ በመገንባት የሚታወቀው አዋሽ ባንክ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በባሌ ዞን በሮቤ ከተማ ያስገነባውን ባለ 4 ወለል ዘመናዊ ሕንጻ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች በተገኙበት በድምቀት በማስመረቅ ለአገልግሎት አብቅቷል፡፡
የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ባላቸው የቱሪስት መስህቦችና በምርታማነቱ በሚታወቀው የባሌ ዞን መዲና በሆነችው የሮቤ ከተማ የተገነባው ይህ ህንጻ የተገነባበት አካባቢ ለንግድና ለተለያዩ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች ተፈላጊ ሥፍራ በመሆኑ ለሀገሪቱ ብሎም ለክልሉ ያለው የኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

Feb 12, 2025 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
124.9998 127.4998
GBP
153.3074 156.3735
EUR
135.5371 138.2478
JPY
0.7393 0.7541
SAR
30.0824 30.6841
AED
30.7258 31.3403
CAD
81.5563 83.1874
CHF
135.5787 138.2902
NOK
10.1355 10.3382
DKK
16.4011 16.7291