አዋሽ ባንክ “አዋሽ ለሁሉም” የተሰኘ ዲጂታል አነስተኛ የብድር አገልግሎት ይፋ አደረገ

ህዳር 24 ፣ 2016 ዓ.ም (አዲስ አበባ)፣ አዋሽ ባንክ “አዋሽ ለሁሉም” የተሰኘ አነስተኛ የብድር አገልግሎት የሚያገኙበት ዲጂታል የብድር አገልግሎት በዛሬው እለት የተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት አካላት እና እንግዶች በተገኙበት በኢሊሊ ሆቴል ይፋ አድርጓል።

በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፉና ዘመኑን የዋጁ የባንክ አገልግሎቶችን በመስጠት ተደራሽነቱን በማስፋት ላይ የሚገኘው አዋሽ ባንክ የደንበኞቹን ፍላጎት ለማርካት ደንበኞች ባሉበት ሆነው አነስተኛ የብድር አገልግሎት የሚያገኙበት “አዋሽ ለሁሉም” የተሰኘውን አገልግሎት እንዲሁም የሳኮስ አይቲ ሶሉዩሽን (SACCOs IT Solution) ቴክኖሎጂ ዛሬ ይፋ ሆኗል።

በሥነ-ስርዓቱ ላይ የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እንደገለፀት አዋሽ ባንክ በኢንዱስትሪው ውስጥ ያለውን የመሪነት ስፍራውን ይዞ እንዲቀጥልና የደንበኞቹን ፍላጎት ለማሟላት በየጊዜው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ተግባራዊ እንደሚያደርግ አመላክተዋል፡፡

Oct 17, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
119.0155 121.3958
GBP
146.3141 149.2403
EUR
129.0483 131.6293
AED
29.3241 29.9105
SAR
28.7101 29.2843
CHF
129.3940 131.9819

Exchange Rate
Close