News

ለክቡራን የአዋሽ ባንክ ባለአክሲዮኖች፣ ደንበኞች እና የአዋሽ ባንክ ማህበረሰብ በሙሉ! እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን! Kabajamtoota Abbootii Aksiyoonaa, Maamiltootaafi Hawaasa Baankii Awaash Hundaaf Baga Gammaddan, Baga Gammanne!

የባንካችን የተከፈለ ካፒታል ብር 10 ቢሊዮን /አስር ቢሊዮን/ ደረሰ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ነባር የግል ባንኮች በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ሊደርሱበት ይገባል ብሎ ያስቀመጠውን የ5 ቢሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል መጠን አዋሽ ባንክ በእጥፍ በመብለጥ የመጀመሪያው የግል ባንክ ሆኗል፡፡ ለዚህም የባንኩን ባለአክሲዮኖች፣ ደንበኞች እና መላውን ሕብረተሰብ በሙሉ ባንኩ ከልብ ያመሰግናል፡፡ አሁንም አስተማማኝ እና መሪ የግል ባንክ […]

የአዋሽ ባንክ የባለአክሲዮኖች 26ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ህዳር 18 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሒልተን ሆቴል ተካሄደ፡፡

የአዋሽ ባንክ የባለአክሲዮኖች 26ኛ ጠቅላላ ጉባኤ ህዳር 18 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሒልተን ሆቴል ተካሂዷል፡፡ በስብሰባውም ላይ የአዋሽ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አምባሳደር ዶ/ር ዲባባ አብደታ በተጠናቀቀው የ2020/21 የሂሣብ ዓመት አዋሽ ባንክ በሁሉም የሥራ ዘርፎች አመርቂ ውጤቶችን ማስመዝገቡንና ከግል ባንኮች የመሪነት ሥፍራውን ለተከታታይ ዓመታት ይዞ መቀጠሉን አስረድተዋል፡፡ በባንኩም የ10 ዓመት ፍኖተ ካርታ መሠረት እ.ኤ.አ. […]

አዋሽ ባንክ ከሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ

በመግባቢያ ሰነዱ ላይ በዝርዝር እንደተቀመጠው አዋሽ ባንክ የፋይናንስ አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግና የኤቲኤም የክፍያ ማሽን ተከላ ለማድረግ በሚንቀሳቀስባቸው ቦታዎች ከኮርፖሬሽኑ ጋር በትብብር ከመስራቱም ባሻገር የኮርፖሬሽኑን ሰራተኞች የደሞዝ ክፍያ በባንኩ በኩል ተፈጻሚ እንዲሆንና ሌሎችም በርካታ ነጥቦች ይገኙበታል፡፡

አዋሽ ባንክ እና የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።

አዋሽ ባንክ በሃገራችን እየተስፋፋ የመጣውንና በተለይ ባንኮችን ተጋላጭ የሚያደርገውን በውክልና ሰነዶች የማጭበርበር ወንጀል ለመከላከል የሚያስችለውን የመግባቢያ ሰነድ ከፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ ጋር ነሃሴ 24 ቀን 2013 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል ተፈራርሟል። የመግባቢያ ሰነዱን የፈረሙት የአዋሽ ባንክ ሆል ሴል ባንኪንግ ቺፍ ኦፊሰር አቶ ታደሰ ገመዳ እና የፌዴራል የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ […]

Page 19 of 19
1 17 18 19

[rates_widgest title="EXCHANGE Rate" selected_currencies="USD, GBP, EUR, AED, SAR, CNY,JPY,CHF" more_link="#"]