የ2ኛው ምዕራፍ የ “ታታሪዎቹ” የሥራ ፈጠራ ውድድር የማጠቃለያ ስነ-ሥርዓት ተካሄደ

አዋሽ ባንክ ስራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታትና ተገቢውን የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ ሲያካሂድ የነበረውን የ2ኛው ዙር የ“ታታሪዎቹ” የስራ ፈጠራ ውድድር የማጠቃለያ መርኃ-ግብር በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል በድምቀት አካሂዷል፡፡

በፕሮጀክቱ ላይ በርካታ ወጣቶች በመሳተፍ የቢዝነስ ሙያ ስልጠና ተጠቃሚ ከመሆናቸውም በተጨማሪ ለተከታታይ ሳምንታት ሰፊ የቴሌቪዥን የስርጭት ሽፋን በነበረው የስራ ፈጠራ ሀሳብ ውድድር ላይም በናሙና (prototype) የተደገፈ ስራዎቻቸውን በማቅረብና ብርቱ ፉክክር በማድረግ በዳኞች ውሳኔ መሰረት ከ 1–5ኛ ደረጃ ለወጡ ተወዳዳሪዎች ከ200 ሺህ እስከ 1 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን በተጨማሪም ፕሮጀክታቸውን እውን የሚያደርጉበት እስከ ብር 5 ሚሊዮን ብድር ያለዋስትና እንደ የፕሮጀክታቸው ሁኔታ ይመቻችላቸዋል፡፡

ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎችን ጨምሮ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ሥነ-ስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እንደገለፁት የባንኩ የኮርፖሬት ማህበራዊ ሃላፊነት አካል የሆነው የታታሪዎቹ ፕሮጀክት ለወደፊቱም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመው ይህ የስራ ፈጠራ ውድድር ከሀሳብ ማመንጨት ጀምሮ እስከ ፕሮግራሙ ፍፃሜ ድረስ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

የ2ኛው ዙር የታታሪዎቹ የሥራ ፈጠራ ውድድር ተሸላሚዎችን ይፋ የማድረጊያ መርሐ-ግብር በመጪው እሁድ ጥር 25 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ጀምሮ በፋና ቴሌቪዥን የሚተላለፍ በመሆኑ በእለቱ እንዲከታተሉ ከወዲሁ እናጋብዛለን፡፡

Mar 09, 2026 - EXCHANGE Rate
CurrencyCash and Remittances through AgentsTransaction
BuyingSellingBuyingSelling
USD USD153.2439156.3088153.0141156.0744
GBP GBP207.4951211.6450207.4951211.6450
EUR EUR181.4794185.1090181.4794185.1090
JPY JPY1.01121.03141.01631.0366
SAR SAR43.084043.945743.587744.4595
AED AED44.022344.902744.539545.4303
CAD CAD111.3935113.6214112.6983114.9523
CHF CHF195.6127199.5250197.8906201.8484
NOK NOK14.737615.032413.697013.9709
DKK DKK23.213723.678023.485123.9548
SEK SEK17.027717.368317.226817.5713