አዋሽ ባንክ በዓለም አቀፍ የቁጠባ እና የሪቴል ባንኪንግ ተቋም እንዲሁም የአውሮፓ የቁጠባ እና የሪቴል ባንኪንግ ቡድን በጋራ የሚያዘጋጁትን የWSBI-ESBG አዋርድ አሸናፊ ሆነ።
ይህንኑ ሽልማት በትላንትናው እለት በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ በተካሄደው የWSBI-ESBG የሽልማት መርሃ-ግብር ላይ በመገኘት የባንካችን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው ተቀብለዋል። ባንካችንም ይህን እውቅና ሊያገኝ የቻለው የዘላቂ ልማት ግቦች ትግበራ ላይ የላቀ አፈፃፀም በማስመዝገብ እንዲሁም አርዓያነት ያለቸውን ምርጥ አሰራሮችን በተለያዩ ዘርፎች በማስመዝገቡ ነው። ከነኚህ ዘርፎችም መካከል ፡-
- በአካታች የባንክ አገልግሎት እና ማህበራዊ ተፅዕኖ፣
- በኢኮኖሚያዊ ዕድገት እና አቅም ማጎልበት፣
- በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና የቴክኖሎጂ ፈጠራ እንዲሁም
- ደንበኛ ተኮር የአቅም ግንባታ ማከናወን ይገኙባቸዋል፡፡
ይህ የእውቅና ሽልማት የተገኘው ክቡራን ደንበኞቻችን በባንካችን ላይ ባሳደራችሁት እምነት በመሆኑ በዚሁ አጋጣሚ የላቀ ምስጋናችንን እያቀረብን ለወደፊቱም በበለጠ ልናገለግላችሁ ዝግጁ መሆናችንን በአክብሮት እንገልፃለን፡፡
አዋሽ ባንክ!



















