አዋሽ ባንክ የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለበርካታ ወገኖች ድጋፍ አደረገ፡፡

አዋሽ ባንክ የ2017 ዓ.ም የፋሲካ በዓልን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ እየሱስ ፕሬዝዳንት ክቡር ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ ፣ የሀይማኖት አባቶች እና በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በዛሬው እለት በመካኒሳ መካነእየሱስ ሴምናሪ ውስጥ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች የዓይነትና የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።
በስነ-ስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የባንኩ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እንደገለፁት መጪውን የ2017 ዓ.ም የፋሲካ በዓልን በማስመልከት ቀደም ሲል አዲስ አበባን ጨምሮ በመላዉ ሀገሪቱ ከአንድ መቶ በላይ በሚሆኑ የድጋፍ መስጫ ጣቢያዎች ከአስር ሺህ በላይ ለሚሆኑ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ፣ ጧሪ ለሌላቸዉ አረጋውያን እና ሌሎች ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ከ63 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለበዓሉ የዓይነት እና የገንዘብ ድጋፍ መደረጉን ጠቁመው በቀጣይም ባንኩ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት እያከናወነ በሚገኘው የበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነእየሱስ ፕሬዝዳንት ክቡር ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ በበኩላቸው አዋሽ ባንክ እያደረገ ላለው በጎ ተግባር ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

Mar 09, 2026 - EXCHANGE Rate
CurrencyCash and Remittances through AgentsTransaction
BuyingSellingBuyingSelling
USD USD153.2439156.3088153.0141156.0744
GBP GBP207.4951211.6450207.4951211.6450
EUR EUR181.4794185.1090181.4794185.1090
JPY JPY1.01121.03141.01631.0366
SAR SAR43.084043.945743.587744.4595
AED AED44.022344.902744.539545.4303
CAD CAD111.3935113.6214112.6983114.9523
CHF CHF195.6127199.5250197.8906201.8484
NOK NOK14.737615.032413.697013.9709
DKK DKK23.213723.678023.485123.9548
SEK SEK17.027717.368317.226817.5713