አዋሽ ባንክ እና የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።

አዋሽ ባንክ እና የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ፣ በትብብር ለመሥራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት በዛሬው እለት ማለትም ሐምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም፣ በባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ተፈራርመዋል፡፡

በፊርማው ሥነ ሥርዓት ላይ፣ የአዋሽ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሀይ ሽፈራው እንደገለጹት፣ ባንኩ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት የሆነውን ግብርና ፋይናንስ ለማድረግና ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አስታውቀው፣ ለዚህም በግብርናው መስክ ከተሰማራው የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት በማድረጉ ኩራት ይሰማዋል ብለዋል።

የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም በበኩላቸው፣ ስምምነቱ ኮርፖሬሽኑ ከባንኩ በሚያገኘው ብድር የእርሻ መሣሪያዎችን፣ እንዲሁም የግብርና ግብዓቶች ማጓጓዣ፣ ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎችን ከውጭ በመግዛትና በመገጣጠም ለአርሶ አደሮች፣ ለባለሃብቶች እና በዘርፉ ለተሰማሩ ሌሎች ተጠቃሚዎች በስፋት ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡

አዋሽ ባንክ ከተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር የመግባቢያ ስምምነት በማድረግ በትብብር በመስራት ላይ ይገኛል፡፡

Mar 09, 2026 - EXCHANGE Rate
CurrencyCash and Remittances through AgentsTransaction
BuyingSellingBuyingSelling
USD USD153.2439156.3088153.0141156.0744
GBP GBP207.4951211.6450207.4951211.6450
EUR EUR181.4794185.1090181.4794185.1090
JPY JPY1.01121.03141.01631.0366
SAR SAR43.084043.945743.587744.4595
AED AED44.022344.902744.539545.4303
CAD CAD111.3935113.6214112.6983114.9523
CHF CHF195.6127199.5250197.8906201.8484
NOK NOK14.737615.032413.697013.9709
DKK DKK23.213723.678023.485123.9548
SEK SEK17.027717.368317.226817.5713