አዋሽ ባንክ ባዘጋጀው የረመዳን ኢፍጣር መርሀ-ግብርላይ ለተለያዩ ተቋማት ድጋፍ አደረገ

የማህበራዊ ሃላፊነቱን በመወጣት የሚታወቀው አዋሽ ባንክ፣ የረመዷን ወር ፆምን ምክንያት በማድረግ በሸራተን ሆቴል ባዘጋጀው የኢፍጣር መርሀ-ግብር ላይ ለተለያዩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችእና ተቋማት የ 23.5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ።
በዚህም መሰረት፡

  1. ለኢትዮ ጠቢብ ጠቅላላ ሆስፒታል ለ24 የኩሌሊት ታካሚዎች ለአንድ አመት የኩላሊት እጥበት የሚውል 6.9 ሚሊዮን ብር
  2. ለአሚን ጠቅላላ ሆስፒታል ለ12 የኩሌሊት ታካሚዎች ለአንድ አመት የኩላሊት እጥበት የሚውል 4.6 ሚሊዮን ብር
  3. ለአወሊያ እርዳታ እና ልማት ድርጅት ማጠናከሪያ የሚውል 5 ሚሊዮን ብር እና
  4. ለታላቁ አንዋር መስጂድ የከርሰ ምድር ውሃ ቁፋሮ የሚውል 7 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል።
    ይህም ድጋፍ በተቋማቱ አማካኝነት ለሚረዱ እና ድጋፍ ለሚሹ ማህበረሰብ ክፍል እንዲደርስ ታሳቢ የተደረገ ነው።

Mar 12, 2026 - EXCHANGE Rate
CurrencyCash and Remittances through AgentsTransaction
BuyingSellingBuyingSelling