አዋሽ ባንክና የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በቀጣይ ጊዜያት በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

የመግባብያ ስምምነቱ ዋና አላማ የደንበኞቹን ፍላጎት ለማርካትና ዘመኑን የዋጁ ቀልጣፋ የባንክ አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ በመስጠት ላይ የሚገኘው አዋሽ ባንክ አዳዲስ የባንኪንግ ቴክኖሎጂዎችን በሃገሪቱ አንጋፋ እና በስርጭት ሽፋኑ ግንባር ቀደም የመንግስት የሚዲያ ተቋም ከሆነው ኢቢሲ ጋር በጋራ በመስራት በሰፊው ለማስተዋወቅና እየሰጠ በሚገኘው የባንኪንግ አገልግሎቶች ላይ በቂ ግንዛቤ ለመፍጠር ነው፡፡
በመሆኑ የመግባቢያ ስምምነቱ ለሁለቱ ተቋማት ለአገራችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ለውጥ አብረውና ተደጋግፈው ለመስራት ምቹ መደላድልን የሚፈጥር ነው፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ስምምነቱ የባንኩ አገልግሎቶች በየጊዜው ለህብረተሰቡ እንዲደርሱና ህብረተሰቡም የአገልግሎቶቹ ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻል ነው፡፡ እንደዚሁም ኢቢሲ አገልግሎቱን ለማዘመንና ተደራሽነቱን ለማስፋፋት የሚያደርገውን ጥረት ባንኩ በሚችለው አቅም ሁሉ እንዲያግዘው ይረዳል፡፡

የመግባቢያ ስምምነቱ የተፈረመው በአዋሽ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ በአቶ ፀሐይ ሽፈራው እና በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ በ ዶ/ር ንጉሴ ምትኩ ታህሳስ 19 ቀን 2012 ዓ.ም በረመዳ ሆቴል ነበር::

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Nov 28, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
55.6854 56.7991
GBP
67.1870 68.5307
EUR
60.9588 62.1780
AED
13.7216 13.9960
SAR
13.4363 13.7050
CHF
60.3764 61.5839

Exchange Rate
Close