አዋሽ ባንክና የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በቀጣይ ጊዜያት በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

የመግባብያ ስምምነቱ ዋና አላማ የደንበኞቹን ፍላጎት ለማርካትና ዘመኑን የዋጁ ቀልጣፋ የባንክ አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ በመስጠት ላይ የሚገኘው አዋሽ ባንክ አዳዲስ የባንኪንግ ቴክኖሎጂዎችን በሃገሪቱ አንጋፋ እና በስርጭት ሽፋኑ ግንባር ቀደም የመንግስት የሚዲያ ተቋም ከሆነው ኢቢሲ ጋር በጋራ በመስራት በሰፊው ለማስተዋወቅና እየሰጠ በሚገኘው የባንኪንግ አገልግሎቶች ላይ በቂ ግንዛቤ ለመፍጠር ነው፡፡
በመሆኑ የመግባቢያ ስምምነቱ ለሁለቱ ተቋማት ለአገራችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ለውጥ አብረውና ተደጋግፈው ለመስራት ምቹ መደላድልን የሚፈጥር ነው፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ስምምነቱ የባንኩ አገልግሎቶች በየጊዜው ለህብረተሰቡ እንዲደርሱና ህብረተሰቡም የአገልግሎቶቹ ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻል ነው፡፡ እንደዚሁም ኢቢሲ አገልግሎቱን ለማዘመንና ተደራሽነቱን ለማስፋፋት የሚያደርገውን ጥረት ባንኩ በሚችለው አቅም ሁሉ እንዲያግዘው ይረዳል፡፡

የመግባቢያ ስምምነቱ የተፈረመው በአዋሽ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ በአቶ ፀሐይ ሽፈራው እና በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ በ ዶ/ር ንጉሴ ምትኩ ታህሳስ 19 ቀን 2012 ዓ.ም በረመዳ ሆቴል ነበር::

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Jun 08, 2023 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
54.3861 55.4738
GBP
64.6741 65.9676
EUR
58.2693 59.4347

Exchange Rate
Close